የአውሮጳ ቅጣት
ረቡዕ፣ ሰኔ 7 2009ማስታወቂያ
የአውሮጳ ኅብረት፣ አባል ሀገራት ግሪክ እና ኢጣልያን በመሳሰሉ ሀገራት የሚገኙ በርካታ ስደተኞችን እንዲከፋፈሉ በወሰነው መሠረት ሀገራት ስደተኞችን እየወሰዱ ነው። ይሁን እና እስካሁን ሦስት ሀገራት ስደተኞች ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆኑም። ህብረቱ በነዚህ ሀገራት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ መወሰኑን ትናንት አስታውቋል። ሀገራቱ ግን ውሳኔው የአባል ሀገራትን ሉዓላዊ መብት የሚጥስ ነው ሲሉ ተቃውመዋል። ገበያው ንጉሴ ከብራሰልስ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ