የአውሮጳ ሕብረት በሉካሼንኮ ላይ የያዘዉ የጸና አቋም
ማክሰኞ፣ መስከረም 12 2013ማስታወቂያ
የአውሮጳ ሕብረት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች የቤላሩስ ፕሬዚዳንት የምርጫ ውጤትን እንደማይቀበሉ እና ዕውቅና እንደማይሰጡ በድጋሚ አረጋገጡ። የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ ትናንት በብራሰልስ ባካሔዱት ስብሰባ የፕሬዚዳንቱን የምርጫ ውጤት ውድቅ ከማድረግ ባሻገር ቤላሩሳውያን ለዴሞክራሲ የሚደርጉትን ትግል እንደሚያደንቁ እና እንደሚደግፉ ገልጸዋል። የትናንትናው የህብረቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ስብሰባ የሊቢያ ጉዳይ በተናጥል እንዲሁም ከአፍሪካ ጋር ስለሚኖረው ቀጣይ የግኙነት ምዕራፍ መክሮ ውሳኔ አስተላልፏል ።
ገበያው ንጉሴ
ታምራት ዲንሳ
እሸቴ በቀለ