1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአንጋፋዎቹ አመራሮች ሞት እና ህወሓት

ሐሙስ፣ ጥር 6 2013

ህወሓት ባደረገው የትጥቅ ትግል እና ከዚያም በኋላ ሥልጣን ይዞ ኢትዮጵያን በመራባቸው ዓመታት ቁልፍ ሚና የነበራቸው የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ምኒስትር ስዩም መስፍን፣ አቶ አባይ ጸሀዬ እና አቶ ዘርዓይ አስገዶም መገደላቸውን መንግሥት አስታውቋል። አቶ ስብሐት ነጋ እና አቶ አባይ ወልዱን የመሳሰሉ ታስረዋል። ይኸ በህወሓት ላይ ምን ጉዳት ያስከትላል?

https://p.dw.com/p/3nvIl
Äthiopien nach TPLF Meeting
ምስል DW/M. Haileselassie

ከቻላቸው ታደሰ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

የህወሓት መሥራች የሆኑት የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ምኒስትር አቶ ስዩም መስፍን፣ የቀድሞው የፌድራል ጉዳዮች ምኒስትር በአንድ ወቅት ደግሞ የጠቅላይ ምኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ የነበሩት አቶ አባይ ጸሀዬ መገደላቸውን የኢትዮጵያ ጦር ትናንት አስታውቋል። ቀደም ብሎ ሌላው ጉምቱ የህወሓት ፖለቲከኛ አቶ ዘርዓይ አስገዶም መገደላቸው ተገልጾ ነበር። ከዚህ በተጨማሪ አቶ ስብሐት ነጋ እና አቶ አባይ ወልዱን የመሳሰሉ ፖለቲከኞችም ታስረዋል። ይኸ በህወሓት ላይ ምን ያክል ጉዳት ያስከትላል? ወደ ስቱዲዮ ከመግባቴ በፊት የፖለቲካ ተንታኙ ቻላቸው ታደሰን አነጋግሬዋለሁ።

እሸቴ በቀለ

ኂሩት መለሠ