የአቶ አበረ ሥርዓተ-ቀብር
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 28 2013ማስታወቂያ
የቀድሞው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር የአቶ አበረ አዳሙ የቀብር ስርዓት ዛሬ በባሕርዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴደራል ተፈፀመ። አቶ አበረ የክልሉን ፖሊስ በበላይነት በመሩበት ወቅት የኮሚሽኑን አደረጃጀት በማስተካከል አባላቱን ተጠቃሚ አድርገዋል ተብሏል፡፡አቶ አበረ ቀድም ሲል በምክትል መቶ አለቃ ማዕረግ የኢትዮጵያ ፖሊስ ባልደረባ ሆነዉ አገልግለዋል። ኤርትራ ሸምቆ የነበረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና ኋላ የግንቦት ሰባት አባልም ነበሩም።አቶ አረባረ ባሕርዳር ሆስፒታል ዉስጥ ሕክምና እየተደረገላቸዉ ያረፉት ባለፈዉ ማክሰኞ ነዉ።
ዓለምነዉ መኮንን
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ