የአሻጎዳ የኃይ ማመንጫ ሥራ አቁሟል
ረቡዕ፣ ግንቦት 14 2011ማስታወቂያ
ትግራይ ርዕሠ-ከተማ መቀሌ አጠገብ የሚገኘዉ የአሻጎዳ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ተቋም በሙሉ አቅሙ ኃይል ማመንጨት ካቋረጠ ከዓመት ከመንፈቅ እንደበለጠዉ የዓይን ምስክሮችና ባለሙያዎች አጋላጡ።ከስድት ዓመት በፊት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ የተባለዉ ተቋም በተመረቀበት ወቅት 120 ሜጋዋት የኤልክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ነበር።የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል መስሪያ ቤት አገልጎሎት ያቋረጡ ተቋማትን ከማስጠገን ይልቅ የኤሌክትሪክ ኃይል በቁነና (በፈረቃ) ለማደል ወስኗል።የአሻጎዳዉን የኤሌክትሪክ ተቋም የጎበኘዉ የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ እንደዘገበዉ ኤሌክትሪክ ማመንጨት የሚገባቸዉ አብዛኞቹ የተቋሙ መዘዉሮች (ተርባዮኖች) አይሰሩም።
ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ
ነጋሽ መሐመድ
ተስፋአለም ወልደየስ