የአሶሳ፣ የጊምቢ እና ነቀምቴ ነዋሪዎች አዲስ ከሚመሰረተው መንግሥት ምን ይጠብቃሉ?
ቅዳሜ፣ መስከረም 22 2014ማስታወቂያ
በመጪው ሰኞ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም. በኢትዮጵያ አዲስ መንግሥት ሊመሰረት ቀነ-ቀጠሮ ተቆርጧል። የአሶሳ፣ የጊምቢ እና የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ለሕዝብ ሰላም እና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት በትኩረት ሊሰራ ይገባል የሚል አቋም አላቸው። ለህብረተሰቡ ስጋት የሆኑት የጸጥታ ችግሮችን መፍታት፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው መመለስ እና የተዘጉ መንገዶችም ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ ማድረግ ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የሶስቱ ከተሞች ነዋሪዎች ከአዲሱ መንግሥት ከሚጠብቋቸው ጉዳዮች መካከል ይገኙበታል። የዛኑ ያክል ከአዲሱ መንግሥት "ምንም የምንጠብቀው ነገር የለም" የሚሉም ይገኙበታል። የአሶሳ፣ የጊምቢ እና ነቀምቴ ነዋሪዎችን ነጋሳ ደሳለኝ አነጋግሯቸዋል። አስተያየቶቹን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ
ነጋሳ ደሳለኝ
እሸቴ በቀለ