የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መራዘሙና የተቃዋሚዎች አስተያየት
ሐሙስ፣ መጋቢት 21 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስበሰባ የአስቸኳዩ ጊዜ አዋጅ በአራት ወራት እንዲራዘሙ ተቃዋሚዎች ሰላማዊ እንቅስቃሴአቸዉን ፤ የመናገር ነፃነታቸዉን የሚገፍና በወታደራዊ አስተዳደር ስል እንዳለ ነዉ ሲሉ ለዶቼ ቬለ ዛሬ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስበሰባ የአስቸኳዩ ጊዜ አዋጅ በአራት ወራት እንዲራዘም መወሰኑን ተከትሎ ፤ መንግስት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሃገሪቱ ተረጋግታለች የሚለዉ ፕሮፖጋንዳ ነዉ ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ የሽዋስ አሰፋ፤ ትናንት ከመንግስት ጋር በተደረገዉ ቅድመ ድርድር ላይ ፓርቲዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ በማለቱ በድርድሩ መባረሩን ገልፀዋል።
የዓረና ትግራይ ለልአላዊነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብረሃ ደስታ በበኩላቸዉ ፤ የአስቸኳይ ጊዜ መራዘሙ ሲቪል መንግሥቱ ሃገሪቱን ማስተዳደር አለመቻሉን ያረጋገጠ ነዉ። የሕዝብን መብት የሚገድበዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጨርሶ መታወጅ አልነበረበትም ያሉት አቶ ሙላቱ ገመቹ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀ መንበር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለአራት ወራት ስለመራዘሙ በሰጡት አስተያየት «ጠቀሜታ የሌለዉ» ሲሉ ተናግረዋል።
አዜብ ታደሰ
ሸዋዬ ለገሠ