1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪካ የዕድገት እና ዕድል ድንጋጌ የበርካታ ሴቶችን ህይወት እየቀየረ ነው

ቅዳሜ፣ ጥቅምት 20 2014

የአፍሪካ የዕድገት እና ዕድል ድንጋጌ (African Growth and Opportunity Act) የበርካታ ሴቶችን ህይወት በመቀየር ውጤት እያስገኘ ነው ሲሉ በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ አወደሱ ። አምባሳደሯ የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውንና ከፓርኩ ሰራተኞች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል።

https://p.dw.com/p/42Nca
Ambassador Geeta Pasi
ምስል S.Wegayehu/DW

የአምባሳደር ጊታ ፓሲ ጉብኝት በሐዋሳ የኢንዱስትሪ ፓርኮች

የአፍሪካ የዕድገት እና ዕድል ድንጋጌ (African Growth and Opportunity Act) የበርካታ ሴቶችን ህይወት በመቀየር ውጤት እያስገኘ ነው ሲሉ በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ አወደሱ ።

አምባሳደሯ የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውንና ከፓርኩ ሰራተኞች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል።

የኢትዮጲያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የስራ ሃላፊዎቸ በበኩላቸው በውጭ አገራት የሚኖሩ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች ኢትዮጲያ የአፍሪካ የዕድገት እና ዕድል ድንጋጌ እያገኘች ያለው ጥቅም እንዲቋረጥ የሚያደርጉት ውትወታ ተገቢነት የሌለው ድርጊት ነው ብለዋል ።

 ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ 

ታምራት ዲንሳ