1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአሜሪካን የሽብር ጥቃት ማስጠንቀቂያና ኢትዮጵያ  

ረቡዕ፣ ኅዳር 15 2014

ዶቼቬለ ስለ ማስጠንቀቂያው ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ባለስልጣን የከተማዋ ደኅንነት አስተማማኝ ነው ብለዋል።የመንግሥት ኮምኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ የኢትዮጵያውያን ደኅንነት በኤምባሲዎች መግለጫ አይረጋገጥም ሲል መግለጫውን ውድቅ አድርጓል,።

https://p.dw.com/p/43Qdn
Äthiopien Addis Abeba | US Botschaft
ምስል Seyoum Getu/DW

ለአሜሪካን የሽብር ጥቃት ማስጠንቀቂያ የኢትዮጵያ መልስ 

የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ በኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል የሰጠውን ማስጠንቀቂያ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አጣጣሉ።ዶቼቬለ ስለ ማስጠንቀቂያው ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ባለስልጣን የከተማዋ ደኅንነት አስተማማኝ ነው ብለዋል።የመንግሥት ኮምኒኬሽን አገልግሎት በበኩሉ የኢትዮጵያውያን ደኅንነት በኤምባሲዎች መግለጫ አይረጋገጥም ሲል መግለጫውን ውድቅ አድርጓል,። የሽብርተኞቹን ማንነት ከማብራራት የተቆጠበው የአሜሪካ መንግስት መግለጫው የሽብር ጥቃቱ ምናልባትም በጥቂት ማሳሰቢያ አሊያም በድንገት የዲፕሎማቶች ማዕከላት፣ የቱሪዚም እና ማጓጓዣ ስፍራዎች፣ በገበያ ማዕከላት፣ የምዕራባውያን የንግድ ተቋማት፣ መዝናኛ እና የመንግስት መገልገየዎችን ትኩረት ሊያድርግ ይችላል ብሏል።

ስዩም ጌቱ 

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሰ