የአማራና የኦሮሞ ፖለቲከኞች ስምምነትና ተቃዉሞዉ
ዓርብ፣ መስከረም 15 2013ማስታወቂያ
10 የአማራና የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ይወክላሉ የተባሉ ፖለቲከኞች በቅርቡ ባደረጉት ስብሰባ አለመሳተፋቸዉንና ስምምነት አለመፈረማቸዉን ሁለት የኦሮሞ የፖለቲካ ማሕበራት አስታወቁ። በአቶ ዳዉድ ኢብሳ የሚመራዉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ባለሥልጣናት ዛሬ በየፊናቸዉ እንዳሉት በስብሰባዉ ላይ እንዲገኙ አልተጋበዙም፤ አልተሰበሰቡም፣ ተፈረመ የተባለዉን ስምምነትም አያዉቁትምም።
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
እሸቴ በቀለ