የአማራ ክልል ፖሊስ በትግራይ ክልል የሚገኝ ኃይል የለኝም አለ
ዓርብ፣ የካቲት 26 2013ማስታወቂያ
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰሞኑን የአማራ ክልል የፀጥታ ኃይሎች ከትግራይ ክልል ይውጡ የሚለው መግለጫ የአማራ ክልል ባለስልጣናትን አስቆጥቷል። መግለጫውን ተከትሎ በትግራይ ክልል የአማራ ክልል ኃይል እንደሌለ እየገለጹ ነው ። ቀደም ሲል ከሕግ አግባብ ውጪ በሌላ አካል ሲተዳደሩ የነበሩ የአማራ አካባቢዎችን መቆጣጠር መቻላቸውንና ያንን አካባቢ ልቀቁ የሚል ክስ ግን ተቀባይነት እንደሌለው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አበረ አዳሙ በተለይ ለዶይቸ ቬለ (DW) ተናግረዋል።
ዓለምነው መኮንን
ታምራት ዲንሳ
ማንተጋፍቶት ስለሺ