1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኒዎ ናዚ አመለካከት ሰለባ የሆኑት የጀርመን ፖሊሶች

ሐሙስ፣ መስከረም 7 2013

ምዕራባዊ የጀርመን ፌዴራላዊ ግዛት ቬዝት ቫልያን የቀኝ ጽንፈኞችን ፕሮፖጋንዳ በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ሲያስተላልፉ ነበር የተባሉ 29 የፖሊስ አባላት ከስራቸው ታገዱ። ፖሊሶቹ ዋትስ አፕ የተባለውን የማህበራዊ መገናኛ ዘዴ በመጠቀም የኒዎ ናዚ አስተሳሰብን የሚደግፉ የተለያዩ መረጃዎችን ሲያስተላልፉ ነበር ተብሏል።

https://p.dw.com/p/3iccu
Deutschland Berlin | Polizisten vor der Charité
ምስል Getty Images/S. Gallup

በምዕራባዊ የጀርመን ግዛት የቀኝ ጽንፈኞች ሰለባ የሆኑ ፖሊሶች

 

በምዕራባዊ የጀርመን ፌዴራላዊ ግዛት ቬዝት ቫሊያን የቀኝ ጽንፈኞችን ፕሮፖጋንዳ በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ሲያስተላልፉ ነበር የተባሉ 29 የፖሊስ አባላት ከስራቸው ታገዱ።ፖሊሶቹ ዋትስ አፕ የተባለውን የማህበራዊ መገናኛ ዘዴ በመጠቀም የኒዎ ናዚ አስተሳሰብን የሚደግፉ የተለያዩ መረጃዎችን ሲያስተላልፉ ነበር ተብሏል። ከሥራቸው የታገዱት ፖሊሶቹ ከሙያ ስነምግባር ባፈነገጠ ክልክል ተግባር ላይ በመሰማራታቸውም ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ይልማ ሃይለሚካኤል

ታምራት ዲንሳ 

አዜብ ታደሰ