1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የችኩንጉኒያ ወረርሽ በድሬዳዋ

ዓርብ፣ ነሐሴ 17 2011

ከሁለት ሳምንት በፊት ነዋሪዎችን መልከፍ እንደጀመረ የሚታመነዉ ወባ መሠል በሽታ በአጭር ጊዜ፣ በመላዉ ከተማይቱ ተሰራጭቷል።

https://p.dw.com/p/3OOLx
Malaria Äthiopien Chikungunia
ምስል DW/M.Tekeleu

ትንኝ የመራባት መዘዝ በድሬዳዋ

ዕዉቁ ኢትዮጵያዊ ድምፃዊ ዓሊ ቢራ «ድሬዳዋ እየኖርን ጅቡቲ ምንያደርግልናል» እያለ በያዚያ በራቀዉ ዘመን ከጅቡቲ ጋር ያነፃፀራት ምሥራቃዊቱ ኢትዮጵያዊት ከተማ ድሬዳዋ፣ ዛሬ ትንኝ ማጥፋት አቅቷት ችኩንጉኒያ ለተባለ ወረርሽኚኝ የነዋሪዎችዋን ጤና እየገበረች ነዉ። ከሁለት ሳምንት በፊት ነዋሪዎችን መልከፍ እንደጀመረ የሚታመነዉ ወባ መሠል በሽታ በአጭር ጊዜ፣ በመላዉ ከተማይቱ ተሰራጭቷል። የድሬዳዋዉ ወኪላችን መሳይ ተክሉ እንደታዘበዉ ችኩንጉኒያ ድሬዳዋ ዉስጥ ያላንኳኳዉ ቤት፣ ያላተኮሰዉ  ሰዉ ማግኘት ሲበዛ ከባድ ነዉ። የከተማይቱ ጤና ቢሮ እንደሚለዉ እስከትናንት ድረስ በትንሽ ግምት ከ7ሺሕ በላይ ሰዉ በበሽታዉ ተለክፏል። የሞተ ስለሞኖር አለመኖሩ ግን እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

,መሳይ ተክሉ

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ