1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታጣቂዎች ጥቃት በመተከልና በወለጋ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 7 2013

በዞኑ በተለይ ቡለን ወረዳ ባለፈዉ ሳምንት ቅዳሜ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭትና ጥቃት በትንሽ ግምት 14 ሰዎች ተገድለዋል።በኦሮሚያ ክልል  ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳም ከትናት በስቲያ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የሰው ህይወት ማለፉን እና በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል

https://p.dw.com/p/3wUUA
Karte Äthiopien Metekel EN

በመተከል ዞን ጋብ ያለዉ ግጭት አገረሸ

በበኒሻጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ባለፉት ጥቂት ወራት ጋብ ብሎ የነበረዉ የጎሳ ግጭትና ጥቃት ሰሞኑን ማገርሸቱን የአካባቢዉ ነዋሪዎች እየተናገሩ ነዉ።በዞኑ በተለይ ቡለን ወረዳ ባለፈዉ ሳምንት ቅዳሜ ጀምሮ በተቀሰቀሰ ግጭትና ጥቃት በትንሽ ግምት 14 ሰዎች ተገድለዋል።በኦሮሚያ ክልል  ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳም ከትናት በስቲያ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የሰው ህይወት ማለፉን እና በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ ሰሞኑን በሁለቱ ወረዳዎች በደረሰ ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር  ከ20 በልጧል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ