1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የታሰሩ የባልደራስ አመራር ለምርጫ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 17 2013

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በቀጣዩ ምርጫ በእጩነት እንዳይቀርቡ ተጥሎባቸው የነበረውን ክልከላ ትናንት ሻረ።

https://p.dw.com/p/3twDf
Der Parteiführer von Balderas traf sich mit Bewohnern von Bahrdar
ምስል DW/A. Mekonnen

«የሕግ አፈፃፀሙ ልዩ ልዩ አማራጮች ይኖሩታል»

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በቀጣዩ ምርጫ በእጩነት እንዳይቀርቡ ተጥሎባቸው የነበረውን ክልከላ ትናንት ሻረ። ውሳኔው ከሕግ አንፃር ተገቢ ነው ያሉ አንድ የሕግ ጠበቃና አማካሪ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፍርድ ቤቱ ብይን አስገዳጅ በመሆኑ የማስፈፀም ግዴታ ይኖርበታል ብለዋል። አመራሮቹ እጩ ሆነው ተመዝግበው፣ በምርጫውም ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ከሆነ የሕግ አፈፃፀሙ ልዩ ልዩ አማራጮች እንደሚኖሩት ገልፀዋል።


ሰለሞን ሙጬ


ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ