የቱኒዝያ ጠ/ሚ ለፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በጩነት ቀረቡ
ዓርብ፣ ነሐሴ 3 2011ማስታወቂያ
የቱኒዝያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሱፍ ቻሃድ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆን እንደሚፈልጉ ተሰማ። ቻሃድ የፊታችን መስከረም 4፣2011 በቱኒዝያ በሚካሄደዉ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ለመወዳደር በእጩነት እንደሚቀርቡ ዛሬ ይፋ አድርገዋል። ቻሃድ እስካሁን ለፕሬዚዳንትነት በእጩነት ከቀረቡት መካከል ስልጣኑን ይረከባሉ ተብሎ የታመነባቸዉ ናቸዉ ተብሎአል። በቱኒዝያ ለፊታችን መስከረም ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የተጠራዉ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን ፕሬዚደንት የቤጅ ሳኢድ ኤስቢስን ቦታ ለመተካት መሆኑ ይታወቃል።
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሠ