የተከለሰው መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ማዕቀፍ ይፋ ሆነ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 2 2012ማስታወቂያ
የፌዴራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለአምስት አመታት ተግባራዊ የሚደረግ ለአንድ አመት የከለሰውን የመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ፓኬጅ ዛሬ አስተዋውቋል። የኢትዮጵያ መሰረታዊ የጤና አገልግሎት አቅርቦት መከላከልን መሰረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ በማሳካት ረገድ በተገልጋዮች ዘንድ ለቅሬታ የተጋለጠ ነው።
ክለሳው ተመጣጣኝና ጥራቱ የተጠበቀ የጤና አገልግሎትን በመዘርጋት በሃገሪቱ የበሽታን ጫና የመቀነስ፤ የጤና ዘርፉን በማሻሻል፣ መሰረተ ልማቶችን በመዘርጋት ህዝቡን ከበሽታ የመጠበቅ፤ የጤና አገልግሎት ስርአቱን ውጤታማነት የማሻሻል እና በዘርፉ ላይ ህዝቡ ተሳትፎው እንዲያድግ እና በውሳኔ አሰጣጡ ላይ ተሳታፊ እንዲሆን የማስቻል አላማዎች ያሉት ነው።
ሰለሞን ሙጬ
ተስፋለም ወልደየስ
አዜብ ታደሰ