የተቃዋሚ ፓርቲዎች ወቀሳ
ዓርብ፣ ነሐሴ 17 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅርቡ ያስረቀቀዉን የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕግ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በድጋሚ ተቃወሙት።የ57 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተወካዮች ዛሬ በጋራ በጠሩት ጋዜጣዊ ጉባኤ እንዳሉት መንግሥትና ገዢዉ ፓርቲ የሚከተሉትን መርሕ «አግላይ» እና «ገፊ» በማለት ነቅፈዉታል። የምርጫና የተቃዋሚ ፓርቲዎች ረቂቅ ሕግ 48 አንቀፆች እንዲሻሻሉ ላቀረቡት ጥያቄ እስካሁን ተገቢ መልስ እንዳላገኙም የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ ተወካዮች አስታዉቀዋል። የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን ጉዳይ አማካሪ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ ግን ረቂቁ «የተወሰነ» ያሉት ማሻሻያ ተደርጎበታል ባይናቸዉ። ከተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አብዛኞቹ ለመጪዉ ዓመት የተያዘዉ የምርጫ ጊዜ እንዲራዘም ጠይቀዋልም።
ዮሕንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ