1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተራዘመው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት

ዓርብ፣ ሐምሌ 16 2013

የትግራዩ ጦርነት ኢትዮጵያ በቃጣናው ላይ ፍላጎት ካላቸው ከውጭ ኃይላት ጋር የምታደርግ የውክልና ጦርነት ነው ያሉት ባለሙያው፤ ተራዝሞ ለወራት የቆየው ወደ ዲፕሎማሲ ጦርነት በመቀየሩ ነውም ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3xx0x
Äthiopien Tigray-Krise
ምስል Yasuyoshi Chiba/AFP/Getty Images

የሕግ ባለሙያ እይታ

ከሳምንታት ወዲህ እንደ አዲስ በማገርሸት ሌላ ምዕራፍ የያዘው የትግራይ ክልል ጦርነት እልባት አልባ የሆነው በውጭ ሃገራት ጣልቃ ገቢነት ነው ሲሉ ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያ ገለጹ። የትግራዩ ጦርነት ኢትዮጵያ በቃጣናው ላይ ፍላጎት ካላቸው ከውጭ ኃይላት ጋር የምታደርግ የውክልና ጦርነት ነው ያሉት ባለሙያው፤ ተራዝሞ ለወራት የቆየው ወደ ዲፕሎማሲ ጦርነት በመቀየሩ ነውም ብለዋል። አሁን ላይ በሁለቱም ወገኖች በኩል ተጨማሪ ኃይል እያሰለፈ የሚገኘው ይኽ ጦርነት የተሻለ እልባት የታጣለትን አስገዳጅ በመሆኑ እንደሆነም አስተያየታቸውን አክለዋል።

ስዩም ጌቱ 

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ