1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተመድ የረድኤት ሠራተኞችና የኢትዮጵያ መንግሥት አቋም 

ረቡዕ፣ ኅዳር 30 2013

ሠራተኖቹ  በቁጥጥር ስር የዋሉትና ጥይት የተተኮሰባቸው ሁለት የተከለከሉ ኬላዎችን አልፈው ወደ ሶስተኛዉ በመሄዳቸው መሆኑን  የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን  ትናንት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል ።

https://p.dw.com/p/3mUe1
Äthiopien | Unruhen | Redwan Hussein, ein Sprecher des Amtes des Premierministers
ምስል Minasse Wondimu Hailu/AA/picture alliance

የተመድ የረድኤት ሠራተኞችና የኢትዮጵያ መንግሥት አቋም 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የረድኤት ሠራተኞች፣በትግራይ ክልል የኢትዮጵያ መንግሥት ከፈቀደላቸው ስፍራ ውጭ ፣ኬላ ጥሰው በማለፍ ጭምር ለመግባት ባደረጉት ሙከራ ተኩስ ተከፍቶባቸው መያዛቸውን መንግሥት አስታውቋል።ሠራተኖቹ  በቁጥጥር ስር የዋሉትና ጥይት የተተኮሰባቸው ሁለት የተከለከሉ ኬላዎችን አልፈው ወደ ሶስተኛዉ በመሄዳቸው መሆኑን  የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ፍሰት ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን  ትናንት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል ።እንዲህ ያለው ሙከራ በድርጅቱ እውቅና የተፈፀመ እንደማይሆን ግምታቸውን ለዶቼቬለ የገለፁ አንድ የሕግ ባለሙያ ሠራተኛቹ በተለይ ዋነኛ የሕወሓት ተፈላጊ አመራሮች ባሉበት አካባቢ ይህንን አድርገው ከሆነ የሀገር ሉአላዊነትን የሚጋፋ እና አደገኛ አካሄድ ነው ብለዋል።ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል።
ሰሎሞን ሙጬ 
ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ