የብሪታንያ አዲስ ሕግና ስደተኞች
ረቡዕ፣ መጋቢት 6 2009ማስታወቂያ
የብሪታንያ መንግሥት በሐገሩ የሚኖሩ ስደተኞችን የሚቆጣጠር፤ የሚቀጣና ወደ ሐገራቸዉ የሚመልስበት አዲስ ደንብ አወጣ።ባለፈዉ ሳምንት የተደነገገዉ ሕግ የጥገኝነት ጊዚያዊ ፈቃድ አግኝቶ የሚኖር ስደተኛ ቋሚ መኖሪያ ፈቃድ ሲጠይቅ ጥገኝነት የተሰጠበት ምክንያት ዳግም እንዲመረመር የሚያስገድ ነዉ።በአዲሱ ደንብ መሠረት ቋሚ መኖሪያ የሚጠይቀዉ ስደተኛ ከለላ አያስፈልገዉም ተብሎ ከታመነ ወደ መጣበት ሐገር እስከመጋዝ የሚያደርስ ቅጣት ይጣልበታል።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ ዘገባ ልካልናለች።
ሐና ደምሴ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ