1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የበረሐ አንበጣ ጉዳት በኢትዮጵያ

ዓርብ፣ መስከረም 22 2013

በቀይ ባህር ዳርቻዎች እንደተፈለፈለ የሚገመተዉ የአንበጣ መንጋ ባለፉት ሁለት  ዓመታት ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የግብርና ምርት 3.5 ሚልዮን ኩንታል የሚሆነውን ማውደሙን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡

https://p.dw.com/p/3jLz1
Kenia Heuschreckenplage
ምስል Reuters/B. Ratner

የአንበጣ መንጋ ሥርጭቱ፣ ጉዳቱና ሥጋቱ

 የአፋር፣ የአማራና የትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎችን የወረረዉ የበረሃ አንበጣ መንጋ አሁንም በሰብልና ደን ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገበሬዎችና የግብርና ባለሥልጣናት አስታወቁ። በቀይ ባሕር ዳርቻዎች እንደተፈለፈለ የሚገመተዉ የአንበጣ መንጋ ባለፉት ሁለት  ዓመታት ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የግብርና ምርት 3.5 ሚልዮን ኩንታል የሚሆነውን ማውደሙን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡ መንጋዉን በፍጠነት መከላከል ካልተቻለ በዘንድሮዉ የምርት ዘመንም  ከፍተኛ ሰብልና ደን ያጠፋል የሚል ሥጋት አሳድሯል። የግብርና ሚኒስቴር ባለሥልጣናት እንደሚሉት ግን መሥሪያ ቤታቸዉ የአንበጣዉን ሥርጭትና የሚያደርሰዉን ጉዳት ለመከላከል እየጣረ ነዉ። ግብርና ሚንስቴር ለሚያደርገዉ ጥረት የዓለም የእርሻና ምግብ ድርጅት (FAO) ድጋፍ እንዳልተለየዉም ባለሥልጣናቱ አስታዉቀዋል።

ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ 

ነጋሽ መሐመድ