የስደተኞች መስመጥ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 8 2011ማስታወቂያ
አፅቢ-ወንበራ ምስራቅ ትግራይ የምትገኝ ወረዳ ናት። ሰሞኑን አብዛኛ ሕዝቧ ሐዘን ተቀምጧል። ምክንያት? ወደ አረብ ሐገር ለመሰደድ ከቤታቸዉ ከወጡ የወረዳዉ ወጣቶች በትንሽ ግምት 40ዉ አደን ባሕረ-ሰላጤ ሰጥመዉ ሞቱ። ባለፈዉ መጋቢት 28 አነስተኛ ጀልባ ተሳፍረዉ ከጅቡቲ ወደ የመን በመቅዘፍ ላይ እንዳሉ ሰጥመዉ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 70 ይደርሳል ነዉ የተባለዉ። ከሟቾቹ ቢያንስ አርባዉ የአንድ ወረዳ ወጣቶች ናቸዉ። የአፅቢ ወንበራ። ኢትዮጵያዊ ወጣት አደጋ እንደሚገጥመዉ እያወቀ በብዛት የመሰደዱ ሰበብ ምክንያት ዛሬም እያነጋገረ ነዉ።
ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ
ነጋሽ መሐመድ
ማንተጋፍቶት ስለሺ