1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስቅለት አከባበር በኢትዮጵያ 

ዓርብ፣ ሚያዝያ 22 2013

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን የሃይማኖት አባቶችና ምዕመናን ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን እለት በስግደትና በፆም በፀሎት አክብረዉት ዉለዋል። ርእሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስና ምዕመናን በታደሙበት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ የምህላና የፀሎት ሥነ-ስርዓት ተከናውኗል።

https://p.dw.com/p/3soeF
Äthiopien I Orthodoxer Freitag in Addis Ababa
ምስል Seyoum Getu/DW

ምእመናን በስግደት እና በፆም በፀሎት ዉለዋል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን እና ምዕመናን ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን እለት በስግደት እና በፆም በፀሎት አክብረዉት ዉለዋል። ቤተክርስቲያኒቱ ርእሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ እና ምዕመናን በታደሙበት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ የምህላና የፀሎት ሥነ-ስርዓት ተከናውኗል። ርእሰ-ሊቃነጳጳሳቱ በዚሁ ወቅት ሃይማኖታዊ ትምህርት እና ቡራኬንም ሰጥተዋል። በሃማኖታዊ ስርዓቱ የታደሙ ምዕመናንም ለወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ በአንድነት መቆምና አብዝቶ መፀለይ ይገባልም ብለዋል፡፡

ሥዩም ጌቱ

አዜብ ታደሰ 

ነጋሽ መሐመድ