1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም የሴቶች ቀን

ሰኞ፣ የካቲት 29 2013

የሴቶች መብትና እኩልነት የሚዘክረው የዓለም የሴቶች ቀን  ዛሬ ማለትም በጎርጎሮሲያኑ መጋቢት 8 በተለያዩ የዓለም ሃገራት ታስቦ ዉሏል።  እንደ ፓኪስታን፣ አውስትራሊያ እና ቱርክ ባሉ ሀገራት ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች  አደባባይ በመውጣት በሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት አውግዘዋል ፣ ፆታዊ እኩልነታቸው እንዲከበርም  ጠይቀዋል።

https://p.dw.com/p/3qLbf
Äthiopien Coronavirus l Straßenverkauf - Mutter versorgt Familie
ምስል Solomon Muchi/DW

የዓለም የሴቶች ቀን

    

የሴቶች የኑሮ ትግልና ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን 

የሴቶች መብትና እኩልነት የሚዘክረው የዓለም የሴቶች ቀን  ዛሬ ማለትም በጎርጎሮሲያኑ መጋቢት 8 በተለያዩ የዓለም ሃገራት ታስቦ ዉሏል።  እንደ ፓኪስታን፣ አውስትራሊያ እና ቱርክ ባሉ ሀገራት ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች  አደባባይ በመውጣት በሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት አውግዘዋል ፣ ፆታዊ እኩልነታቸው እንዲከበርም  ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ ውስጥም ይህንን ቀን አስመልክቶ ትናንት እሁድ የመንግስት አመራሮች፣ ታዋቂ አትሎቶች እና አርቲስቶች እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች የተካፈሉበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ላይ ተካሂዷል። እንደዛም ሆኖ ይህ ቀን ለምን ታስቦ እንደሚውል የማያውቁ ሴቶች አሉ። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰለሞን ሙጬ ዝቅተኛ ገቢ በሚያስገኝ ሥራ ላይ ተሰማርተው ሕይወትን የሚመሩ ሦስት ሴቶችን ሥለ ሥራና አኗኗራቸው ጠይቆ ተከታዮን ዘገባ ልኮልናል።
ሰለሞን ሙጬ
ልደት አበበ
አዜብ ታደሰ