1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ እና ምርጫ ቦርድ 

ረቡዕ፣ ጥቅምት 5 2012

የሲዳማ ብሄር ሕዝበ ውሳኔ ሚስፈጸሚያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት በበኩሉ በቦርዱ የተጠየቀው የህግና አስተዳደራዊ ማዕቀፎች ቢዘገዩም ዝርዝር ህጎች እያዘጋጀ እንደሆነ ገልጿል።በቦርድ ያደረገው የድምፅ ማስጫ ቀን ሽግሽግ ምክንያታዊ በመሆኑ ተቃውሞ እንደሌለው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ( ሲአን )አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3RP0r
Äthiopien Stadtansicht Awassa
ምስል DW/S. Wegayehu

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ እና ምርጫ ቦርድ 

የኢትዮጲያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ብሄር ህዝበ ውሳኔን ለማስፈጸም ያስችለኛል በሚል የጠየቃቸው የሕግና አስተዳደራዊ ማዕቀፎች እስከአሁን ከክልሉ አልቀረበልኝም ሲል አስታውቋል። የሲዳማ ብሄር ህዝበ ውሳኔ ሚስፈጸሚያ ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት በበኩሉ በቦርዱ የተጠየቀው የህግና አስተዳደራዊ ማዕቀፎች ቢዘገዩም ዝርዝር ህጎች እያዘጋጀ እንደሆነ ገልጿል።በቦርድ ያደረገው የድምፅ ማስጫ ቀን ሽግሽግ ምክንያታዊ በመሆኑ ፓርቲያቸው ተቃውሞ እንደሌለው የገለፁት የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ( ሲአን ) ዋና ጸሀፊ በበኩላቸው ይቅረቡ የተባሉት የህግና አስተዳደራዊ ማዕቀፎች ግን ከአገሪቱ ህገ መንግስታዊ መብቶች ጋር ይቃረናሉ የሚል እምነት የለኝም ብለዋል።ዝርዝሩን የሀዋሳው ዘጋቢያችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ልኮልናል።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ