1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰባት ፖለቲካ ፓርቲዎች ሥምምነት

ሰኞ፣ መስከረም 7 2011

ብሔር እና የፖለቲካ አመለካከትን ተኮር ያደረገ ነዉ የተባለዉን በኢትዮጵያ የሚታየዉን ግጭት ለመታገል በሃገር ዉስጥ ያሉና ከዉጭ የገቡ በአጠቃላይ ሰባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በኅብረት ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸዉ ተሰማ። የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ዛሬ መግለጫም ሰጥተዋል።

https://p.dw.com/p/352cL
Blick aus meinem Fenster Addis Abeba Flash-Galerie
ምስል Solomon Mengist

ግጭቱ የሚቀሰቅሱት ኃይላት ለዉጡን ለማደናቀፍ ያለሙ ናቸዉ

ብሔር እና የፖለቲካ አመለካከትን ተኮር ያደረገ ነዉ የተባለዉን ሰሞኑን በኢትዮጵያ የሚታየዉን ግጭት ለመታገል በሃገር ዉስጥ ያሉና ከዉጭ የገቡ በአጠቃላይ ሰባት የፖለቲካ ፓርቲዎች በኅብረት ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸዉ ተሰማ። ሰባቱ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደገለፁት በኢትዮጵያ የሚታየዉን ችግር ለመቅረፍ ሁለት ቀናት ከተወያዩ በኋላ ዛሬ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። የፖለቲካ ፓርቲ ተጠሪዎቹ እንደገለፁት ግጭትና ብጥብጥ የሚፈጥሩትኃይላት በኢትዮጵያ የሚታየዉን የለዉጥ ሂደት ለማደናቀፍ ነዉ።   

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ