የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎችን የታደጉት የሃይማኖት አባት
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 20 2014ሕወሓት በአማራ ክልል የዋግ ኽምራ ቤሔረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ከተማ በቆየበት ወቅት ኅብረተሰቡ በራብ እንዳይሞትና እንዳይቸገር የዋኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደርና የምዕራብ ካናዳ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ባርናባስ ገንዘብና ምግብ በማሰባሰብ ህዝቡን መታደጋቸውን ተናገሩ፣ አቡነ በርናባስ ሰዎችን በሰውነት ብቻ በመመዘን ያለልዩነት እርዳታ ያደርጉ አንደነበር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ የህወሓት ኃይሎች በሰቆጣ ከተማ በቆየባቸው ከ2 ወራት በላይ ጊዜ ህብረተሰቡ ለከፍተኛ ርሀብ ተጋልጦ መቆየቱን የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለስልጣናት ይናገራሉ።
ይህ ክፉ የርሀብ ጊዜ ሕይወት እንዳያጠፋ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደርና የምዕራብ ካናዳ ሊቀ ጳጳስ አቡነ በርናባስ ከውጫና ከአገር ውስጥ ያለውን ህዝብ በማስተባበር የአምግብ እህልና ገንዘብ በማቅረብ የተቸገሩ ወገኖችን መታደግ መቻሉን ለዶይቼ ቬለ ገልፀዋል። በሁለተኛው ዙር የወረራ ወቅት ቡድኑ አመጣጡ ያስፈራ እንደነበር የተናገሩት አቡነ ባርናባስ ታጣቂዎቹ ክፉ ነገሮችን እንዳይፈፅሙ ከብሔረሰብ አስተዳደሩ አገረስብከት ጋር በመሆን ጥረት ይደረግ ነበር ብለዋል፡፡ በሰሜን ወሎ ወልዲያ ከተማም የክርስትናና የእስልምና አባቶች ያለ ልዩነት በመስራት ከ22ሺህ በላይ የሚሆነውን የከተማዋ ነዋሪ ብድርና እርዳታ በመስጠት በርካታ ህይወት መታደጋቸውን የወልዲያ ሰላም መስጊድ ኮሚቴ አባል ሀጂ ያሲን እንደሪስ ተናግረዋል፡፡
አለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ