የሰሞንኛዉ የመንግሥታቱ ድርጅት መግለጫ «ሚዛናዊ» ተባለ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 19 2013ማስታወቂያ
የተባበሩት መንግስታት ሰሞኑን ኢትዮጵያን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ ድርጅቱ ቀደም ሲል ይዞት የነበረውን አቋም ያጠፈ እና ሚዛናዊ ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ፌደራል ፖሊስ በትግራይ ክልል የደረሱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ምርመራ እያደረጉ ሲሆን አጥፊዎች ላይ ያለምንም ምሕረት ተጠያቂነት ይከተላልም ተብሏል። ሚኒስቴሩ በሳምንታዊ መግለጫው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር አሁንም በአፍሪካ መድረክ እንዲቀጥልና መቃጫ እንዲያገኝ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። የኢትዮ ሱዳን የድንበር ውዝግብ ላይ ምንም አዲስ ነገር የለም ያለው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ጉዳዩ በሰላም ይፈታ የሚለው አቋሟን እንደያዘች መሆኑም ተነግሯል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ