የሰላም ሚኒስቴር ችግሮችን ለመፍታት እየሰራሁ ነዉ አለ
ሐሙስ፣ ጥቅምት 27 2012ማስታወቂያ
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሰላም ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙት ተጠሪ ተቋማት ደፈር ያለ ህግን የማስከበር እርምጃ እንዲወስዱ አሳሰበ። ቋሚ ኮሚቶው የሚኒስቴሩን የሦስት ወራት ስራ ሲገመግም እንዳለው ሃገሪቱን ለማተራመስ የሚጥር የተደራጀ ቡድን አለ ብሏል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽንም ሰራዊቱ በተበታተና ሃኔታ እንድልሚገኝና ስራውን ለማከናወን እየገጠመው ያለውን ጣልቃግብነት ቋመልፕ ኮሚቴው እንዲያውቅለት ጠይቊል። የሰላም ሚኒስቴር በበኩሉ በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ወቅታዊ እና አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ እና መዋቅራዊ እና በሂደት የሚፈቱ በሚል ለይቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። ዝርዝሩን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ሰለሞን ሙጬ ያቀርበዋል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ