የ"ራይድ" መስራች ሽልማት
ዓርብ፣ መስከረም 14 2014ማስታወቂያ
የራይድ ትራንስፖርት መስራችና ሥራ አስፈፃሚ ሳምራዊት ፍቅሩ የምርጥ አፍሪካዊ ቢዝነስ ባለራዕይ ሽልማት አሸናፊ ሆነች። የራይድ መስራቿ አሸናፊ የሆነችው በሃገራቸው የኤኮኖሚ ዕድገት አስተዋፅዖ ያደረጉ ሰዎችን አወዳድሮ ዕውቅናና ሽልማት በሚሰጠው የአፍሪካ ኅዳሴና ዳያስጶራ በተሰኘ ተቋም ነው። ሳምራዊት ሽልማቱን በተቀበለችበት ወቅት ባስተላለፈችው መልዕክት በርካታ ዕንቅፋቶችን በመጋፈጥና በማለፍ ለዚህ መብቃቷን ተናግራለች። የአትላንታዉ ወኪላችን በበይነ መረብ የተካሄደውን ሥነ ስርዓት ተከታትሎ ዘገባ አዘጋጅቶቷል።
ታሪኩ ኃይሉ
አዜብ ታደሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ