1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የምዕራባዉያን መሪዎች ጉባኤ

ሐሙስ፣ መጋቢት 15 2014

የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO)፣ የአዉሮጳ ሕብረትና የቡድን ሰባት (G7) አባል ሐገራት መሪዎች የጀመሩት ጉባኤ አብይ ትኩረት የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ መከላከል ነዉ

https://p.dw.com/p/48zyn
Belgien | Nato-Sondergipfel zum Ukraine-Konflikt
ምስል Eric Lalmand/BELGA/dpa/picture alliance

ተጨማሪ ወታደሮች እንዲሰፍሩ ይወስናሉ ተብሎ ይጠበቃል

             

ዩናይትድ ስቴትስ የምትመራና የምታስተባብራቸዉ የተለያዩ ማሕበራት አባል ሐገራት መሪዎች ዛሬ ብራስልስ-ቤልጂግ ዉስጥ ጉባኤ ተቀምጠዋል።የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO)፣ የአዉሮጳ ሕብረትና የቡድን ሰባት (G7) አባል ሐገራት መሪዎች የጀመሩት ጉባኤ አብይ ትኩረት የዩክሬንና የሩሲያ ጦርነት ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ መከላከል ነዉ።ጉባኤተኞች የኔቶ አባል በሆኑ የምሥራቅ አዉሮጳ ሐገራት ተጨማሪ የአሜሪካ ጦር እንዲሰፍር ይወስናሉ ተብሎም ይጠበቃል።

ገበያዉ ንጉሴን 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ