1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የምርጫ ጊዜ ዉዝግብ

ዓርብ፣ ሐምሌ 26 2011

ምርጫዉ ከዚሕ ቀደም በተያዘዉ የጊዜ ሠለዳ መሠረት በመጪዉ ዓመት ግንቦት አካባቢ መደረግ አለበት-የለበትም የሚል ተቃራኒ አቋም ከያዙ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የሁለቱ ተወካዮች ዛሬ እንዳሉት የጠቅላይ ሚንስትሩ መግለጫ አሻሚ ነዉ።

https://p.dw.com/p/3NFHB
Wahltag in Äthiopien Hosaena
ምስል DW/Y.-G. Egziabhare

የኢትዮጵያ የምርጫ ጊዜ ዉዝግብ

ኢትዮጵያ  አጠቃላይ ምርጫ የሚደረግበት ጊዜ የሐገሪቱን ፖለቲከኞች አሁንም እያወዛገበ ነዉ። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ ትናንት በሰጡት መግለጫዉ ሥለ ምርጫዉ ጊዜ ቁርጥ ያለ መልስ አለመስጠታቸዉ ዉዝግቡ እልባት እንዳያገኝ አድርጎታል። ምርጫዉ ከዚሕ ቀደም በተያዘዉ የጊዜ ሠለዳ መሠረት በመጪዉ ዓመት ግንቦት አካባቢ መደረግ አለበት-የለበትም የሚል ተቃራኒ አቋም ከያዙ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የሁለቱ ተወካዮች ዛሬ እንዳሉት የጠቅላይ ሚንስትሩ መግለጫ አሻሚ ነዉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲስ ያረቀቀዉን የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት ሕግን 33 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትናንት በይፋ ተቃዉመዉታል።

 ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ