1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«የሜርክል ዘመን አላበቃም »

ቅዳሜ፣ ኅዳር 29 2011

የጀርመን ክርስቲያን ዴሞክራት ፓርቲ በጀርመንኛ ምህጻሩ ሴዱኡ ሀምበርግ ላይ ትናንት ስብሰባውን ሲያካሂድ ላለፉት 18 ዓመታት ፓርቲውን በሊቀመንበርነት የመሩት የሀገሪቱ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክልን የሚተካ ሊቀመንበር መርጧል።

https://p.dw.com/p/39kAV
Deutschland CDU-Parteitag in Hamburg Kramp-Karrenbauer
ምስል picture-alliance/dpa/K. Nietfeld

ሜርክልን የተኩት አነግሬት ክራምፕ ካረንባወር

ሜርክልን እንዲተኩ በአብላጫ ድምፅ የተመረጡት የ56 ዓመትዋን አነግሬት ክራምፕ ካረንባወር ቀደም ብለው ፓርቲውን በፀሐፊነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን የሜርክል ቀኝ እጅ መሆናቸው ይነገራል። ለዚህም ይመስላል ሜርክል በሊቀመንበርነትም በመራሂተ መንግሥትነትም መቀጠሉ በቃኝ ብለው ተራውን ለሌሎቹ የፓርቲው አባላት ቢለቁም የክራምፕ ካረንባወር መመረጥ ያው እሳቸው እንዳሉ ያህል ነው የሚል አስተያየት ከፖለቲከኞች እና ከጋዜጠኞች ያስከተለው። የDW ጀርመንኛው ክፍል ባልደረባ የሆነችው ኢንስ ፖል ሜርክል በመራሂተ መንግሥትነት ይቆያሉ ስትል የጻፈውን አስተያየት እና ሃተታ የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል እንደሚከተለው ተርጉሞታል።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል/ኢንስ ፖል

ሸዋዬ ለገሠ