1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የማረቆ ብሄር ተወላጆች የተቃውሞ ሰልፍ በሐዋሳ

ሐሙስ፣ መጋቢት 29 2014

በጉራጌ ዞን የማረቆ ብሄር ተወላጆች ቀደም ሲል ያቀረብነው የልዩ ወረዳ መዋቅር እና የማካለል ጥያቄ ተግባራዊ ይደረግልን ሲሉ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ባካሄዱት ሠላማዊ ሠልፍ ጠየቁ።

https://p.dw.com/p/49cf6
Äthiopien | Anti-Regierungsproteste
ምስል Shewangizaw Wegayehu/DW

ጥያቄያችን ተግባራዊ ይደረግ ብለዋል

በጉራጌ ዞን የማረቆ ብሄር ተወላጆች ቀደም ሲል ያቀረብነው የልዩ ወረዳ መዋቅር እና የማካለል ጥያቄ ተግባራዊ ይደረግልን ሲሉ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ባካሄዱት ሠላማዊ ሠልፍ ጠየቁ። ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ አቶ ሞሣ ዋቤቶ የሰልፉ አላማ የማረቆ ሕዝብ እራሱን በቻለ ልዩ ወረዳ እንዲደራጅ እና ከመስቃን ወረዳ ጋር የሚያዋስኑት 9 ቀበሌያት በሕጋዊ መንገድ እንዲካለሉ ለመጠየቅ ሲሉ ለዶቼ ቬል (DW) ተናግረዋል። ዝርዝሩን የሀዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ልኮልናል።


ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ