የመኢአድ መግለጫ
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 11 2010ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)ም ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፀመዉ ግድያን ግድያ አዉግዟል።የድርጅቱ መሪዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ እስካሁን የደረሰዉ ጥፋት በገለልተኛ ወገኖች ተጣርቶ ጥፋተኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ አሳስበዋል።የመኢአድ ባለሥልጣናት እንደሚሉት የግጭት እና ግድያዉ መሠረታዊ ምክንያት ኢትዮጵያ የምትከተለዉ በጎሳ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሥርዓት ነዉ።በለስልጣናቱ አክለዉ እንዳሉት ሰዉ በማንነቱ መገደል የለበትም።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ አለዉ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ