1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል በርካታ ቦታዎችን መቆጣጠራቸው

ረቡዕ፣ ኅዳር 22 2014

የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የመንግሥት ኃይሎች ድል ቀንቷቸው ወደ ፊት እየገሰገሱ መሆኑን አረጋግጠዋል።

https://p.dw.com/p/43hZd
Äthiopien | Dr. Legesse Tulu - Kommunikationsminister
ምስል Seyoum Getu/DW

የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ መግለጫ

በሰሜን ኢትዮጵያ በቀጠለው ጦርነት የመንግሥት ኃይሎች የጦር ስልታዊ ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው የተባለለት የሰሜን ወሎ ጋሸና እና ሌሎች አከባቢዎችን መቆጣጠራቸው ተገለጸ። የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የመንግሥት ኃይሎች ድል ቀንቷቸው ወደ ፊት እየገሰገሱ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ከሰሜን ወሎ ሁለት ግንባሮች በተጨማሪ በሰሜን ሸዋም የመከላከያ ሠራዊቱ እና ሌሎች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ድል አስመዝግበው የተለያዩ አከባቢዎችን ከህወሃት ኃይሎች ማስለቀቅ መቻላቸውንም አመልክተዋል።

ስዩም ጌቱ 

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ