የመን ጦርነት፤በሽታና ረሐብ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 27 2009ማስታወቂያ
የመንን በሚያወድመዉ ጦርነት የሚፋለሙት ሳዑዲ አረቢያና ተከታዮችዋ በጦርነቱ ለሚደርሰዉ ጥፋት ተጠያቂ እንደሚሆኑ የርዳታ ርድጅት ሠራተኞች አስጠነቀቁ።የተባበሩት መንግሥታት እና ሌሎች ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች እንደሚሉት ጦርነቱ በቀጥታ ከፈጀዉ ሕዝብ በተጨማሪ ለረሐብና ለኮሎራ ያጋለጠዉ ሕዝብ እየሞተ ነዉ።የተባበሩት መንግሥት ድርጅት እንዳስታወቀዉ በኮሌራ በሽታ ብቻ ከሁለት ሺሕ የሚበልጥ ሕዝብ አልቋል።በየዕለቱ በሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ በበሽታዉ ይለከፋል።የርዳታ ድርጅቶች እንደሚሉት በሽታዉ የተከሰተዉ ሳዑዲ አረቢያ የምትመራቸዉ ሐገራት የጦር ጄቶች የቁሻሻ መተላለፊያ ቧምባዎችን፤ ሕንፃና ሆስፒታሎችን በማዉደማቸዉ ነዉ።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ