የመኢአድ ጥሪ
ረቡዕ፣ ሐምሌ 21 2013ማስታወቂያ
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ በአጭሩ ህወሓት ለፍርድ እንዲቀርብ እንዲደረግ ጠየቀ። ድርጅቱ ይህን ያለው የአማራ ክልል የክትት ጥሪን እንደሚደግፍ ዛሬ ባሳወቀበት መግለጫው ነው። የድርጅቱ አመራር አባላት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የፌደራል መንግሥት ህወሓትን በአስቸኳይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሊያስወግድ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። አባላቱም ሀገር የማዳን ባለው ዘመቻ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ