ለ2012 የቀረበው በጀት ፀደቀ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 4 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሚቀጥለው ዓመት የቀረበው የ387 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት ረቂቅ ላይ ዛሬ ተወያየ። ባሳለፍነው ቅዳሜ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ በጀቱ ላይ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። የገንዘብ ሚንሥትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ዛሬ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የበጀት ዝርዝር ላይ ውይይት ተካሂዷል። ለ2012 ዓም የተያዘው በጀት ባለፈው ዓመት ከጸደቀው በጀት የ1 ነጥብ 6 ጭማሪ እንዳለው ሚንሥትሩ ተናግረዋል። ኢኮኖሚው በሚቀጥለው የበጀት ዓመት የተወሰነ መነቃቃት በማሳየት ከዘጠኝ በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ ታሳቢ መደረጉንም አክለው ገልጠዋል። ዮሐንስ ገብረ-እግዚአብሔር ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ-እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ