የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ተዋጊዎች የፈጸሙትን ግፍ አምንስቲ ማጋለጡ
ረቡዕ፣ የካቲት 9 2014ማስታወቂያ
የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ተዋጊዎች ጭና እና ቆቦ ከተሞችን ተቆጣጥረዉ በነበረበት ወቅት በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸዉንና ሴቶችን መድፈራቸዉን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አጋለጠ።ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ዛሬ ይፋ ያደረገዉ የምርመራ ዉጤት እንዳመለከተዉ ታጣቂቹ የ14 ዓመት ታዳጊ ልጃገረድን ሳይቀር ደፍረዋል። የሕወሓት ታጣቂዎች ነፋስ መዉጪያ ከተማን በተቆጣጠሩበት ወቅት በርካታ ሴቶችን አስገድደዉ መድፈራቸዉን ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ባለፈዉ ሕዳር አስታዉቆ ነበር።
ሐይማኖት ጥሩነህ
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሰ