የሐዋሳ የዛሬ ውሎ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 11 2011ማስታወቂያ
የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ርዕሰ ከተማ ሃዋሳ ዛሬ ውጥረት ሰፍኖ ነው የዋለው።ግጭትም እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል። ጸጥታ አስከባሪዎች ከተማይቱን ሲቆጣጠሩ ነው የዋሉት።በሌሎች ከተሞችም ግጭት እና ዘረፋ እንደነበረ ተዘግቧል።የሃዋሳ እና የሌሎች የደቡብ ክልል ከተሞች የዛሬ ውሎ ምን እንደሚመስል አዜብ ታደሰ የሃዋሳውን ወኪላችንን ሸዋንግዛው ወጋየሁን በስልክ አነጋግራዋለች።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
አዜብ ታደሰ