1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዙሪኩ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል

ሰኞ፣ ሐምሌ 29 2011

የቀድሞ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች በእንግድነት የተገኙበት የዘንድሮው ውድድር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የተሻለ እንደነበር አዘጋጆቹ ተናግረዋል።በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኘችው የፓሪስዋ ወኪላችን ሃይማኖት ጥሩነህ እንደታዘበችው በፌስቲቫሉ ሴቶችን የሚያሳትፉ ውድድሮች አልነበሩም።

https://p.dw.com/p/3NMvO
Schweiz äthiopisches Sport- und Kultur-Festival in Zürich
ምስል DW/H. Tiruneh

የዙሪኩ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል

ዙሪክ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ባለፈው ሳምንት የተካሄደው 17 ተኛው «በአውሮጳ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል»ባለፈው ቅዳሜ ተፈጽሟል።በእግር ኳሱ ውድድር «ኢትዮ ቡና ፍራንስ» ተጋጣሚውን የኢትዮ ሆላንድ ቡድን አሸንፎ  የዘንድሮው ሻምፕዮና ሆኗል።በታዳጊ ወጣቶች ዘርፍ በተካሄደው ውድድርም ኢትዮ ፍራንስ አዘጋጁን የኢትዮ ዙሪክ ቡድን አሸንፎ ዋንጫውን ወስዷል። የቀድሞ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች በእንግድነት የተገኙበት የዘንድሮው ውድድር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የተሻለ እንደነበር አዘጋጆቹ ተናግረዋል።በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኘችው የፓሪስዋ ወኪላችን ሃይማኖት ጥሩነህ እንደታዘበችው በፌስቲቫሉ ሴቶችን የሚያሳትፉ ውድድሮች አልነበሩም። ዝርዝሩን ሳምንታዊው የስፖርት መሰናዶ ተጠናቅሮአል።
ሃይማኖት ጥሩነህ 
ኂሩት መለሰ

Schweiz äthiopisches Sport- und Kultur-Festival in Zürich
ምስል DW/H. Tiruneh