1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የሃይማኖቶች ጉባኤ ጥሪ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 27 2013

ጉባኤዉ ዛሬ እንዳስታወቀዉ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረገዉ ጦርነት፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ያለዉ ግጭትና በሌሎች አካባቢዎች ያንዣበበዉ ሥጋት በሐገሪቱ ላይ ከፍተኛ ሰብአዊና ምጣኔ ሐብታዊ ኪሳራ አድርሷል

https://p.dw.com/p/3zpHQ
Äthiopien Addis Abeba | gemeinsame Pressekonferenz religiöster Institutionen
ምስል Solomon Muchie/DW

የኃይማኖት ጉባኤ የድርድርና የፀሎት ጥሪ

ኢትዮጵያን የሚያወድመዉን ጦርነትና ፖለቲካዊ ቀዉስ ለማስወገድ ሁሉም ወገኖች የሚሳተፉበት ነፃና ግልፅ ዉይይት እንዲደረግ የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠየቀ።ጉባኤዉ ዛሬ እንዳስታወቀዉ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረገዉ ጦርነት፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ያለዉ ግጭትና በሌሎች አካባቢዎች ያንዣበበዉ ሥጋት በሐገሪቱ ላይ ከፍተኛ ሰብአዊና ምጣኔ ሐብታዊ ኪሳራ አድርሷል።በተገባደደዉ 2013 ዓመት በየአካባቢዉ የተፈጠረዉ ሰዉ ሠራሽና የተፈጥሮ ቀዉሶች እንዲወገዱም ከጵዋግሜ 1 ጀምሮ ለዓምስት ቀን የሚዘልቅ ብሔራዊ ፀሎት እንዲደረግ አዉጇልም።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ