1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የCDU ጉባዔ

ዓርብ፣ ኅዳር 12 2012

የጀርመን ገዢ ፓርቲ የክርስቲያን ዴሞክራት ሕብረት (CDU-በጀርመንኛ ምሕፃሩ) መሪ ወይዘሮ አነግሬት ክራምፕ-ካረን ባወር የፓርቲ ጓዶቻቸዉ ድጋፍ ካልሰጧቸዉ ሥልጣን እንደሚለቁ አስጠነቀቁ። ጀርመንን ለማነፅና ኃላፊነት ለመቀበል ከፈለጋችሁ እጅጌአችንን እንጠቅልል ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3TZGx
CDU-Bundesparteitag in Leipzig 2019
ምስል picture-alliance/AP Photo/J. Meyer

የጀርመን ገዢ ፓርቲ የክርስቲያን ዴሞክራት ሕብረት (CDU-በጀርመንኛ ምሕፃሩ) መሪ ወይዘሮ አነግሬት ክራምፕ-ካረን ባወር የፓርቲ ጓዶቻቸዉ ድጋፍ ካልሰጧቸዉ ሥልጣን እንደሚለቁ አስጠነቀቁ። የCDUን የረጅም ጊዜ መሪ መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክልን የሚተኩት ክራምፕ ካረን ባወር በሊቀመንበርነት ከተመረጡ ካለፈዉ ዓመት ወዲሕ አንጋፋዎቹ የፓርቲዉ ፖለቲከኞች የአመራር ብቃታቸዉን እየተቹ ነዉ። ክራምፕ ካረንባወር ዛሬ ላይፕዚሽ-ምሥራቅ ጀርመን ዉስጥ ለተሰየመዉ የፓርቲዉ ጉባኤ እንደነገሩት ተቺዎቻቸዉ አደብ ካልገዙ ሥልጣን ለመልቀቅ ዝግጁ ናቸዉ።«ዛሬዉኑ።» አሉ።«እኔ የምፈልጋት ጀርመን እናንተ እንድትሆን ከምትመኟት የተለየች ናት ብላችሁ ካሰባችሁ። ከናንተ ጋር ልጓዝበት የምፈልገዉ መንገድ እናንተ ትክክል ነዉ ብላችሁ ከምታስቡት የተለየ ነዉ ካላችሁ፤ ዛሬዉኑ እንናገረዉ፣ ዛሬዉኑ እናቁመዉ፣ እዚሁ፣ አሁኑኑ።ይሁንና ዉድ ወዳጆቹ፣ ይችን ጀርመንን ከፈለጋችኋት፣ይሕን መንገድ አብረን እንድንጓዝበት ከመረጣችሁ፣ ጀርመንን ለማነፅና ኃላፊነት ለመቀበል ከፈለጋችሁ እጅጌአችንን እንጠቅልል።እዚሁ፣ አሁኑኑ እና እንጀምር።»የ57 ዓመቷ ፖለቲከኛ እንደ ጎርጎሪያኑ አቆጣጠር በ2021 በሚደረገዉ ምርጫ ወይዘሮ አንጌላ ሜርክልን ተክተዉ ለመራሔ መንግስትነት ይወዳደራሉ።

ነጋሽ መሐመድ 

አዜብ ታደሰ