1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ2011 ረቂቅ በጀት ፀደቀ

ዓርብ፣ ሰኔ 29 2010

የኢትዮጵያ ምክር ቤት የ2011 ረቂቅ በጀትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ በተገኙበት ፀደቀ። የኢትዮጵያ መንግሥት በመጪዉ የበጀት ዓመት አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንደማይጀምር ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ አስታዉቀዋል።

https://p.dw.com/p/30y8b
Äthiopien - Parlament
ምስል DW/Y. Gebregziabher

የ 2011 በጀት ዓመት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይጀመርም

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ዛሬ በምክር ቤት ባደረጉት ንግግር በየሰበብ አስባቡ በየቦታዉ የሚታየዉ ግጭት አስመልክቶም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ እንደግብርናዉ ሁሉ የትምህርቱም ዘርፍ ትኩረት ሊሰጠዉ እንደሚገባ ገልፀዋል። በሃገሪቱ የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍ «ፍኖተ ካርታ» እየተጠናቀቀ መሆኑንና በቅርቡ ለዉይይት ቀርቦ ስራ ላይ እንደሚዉል ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ሰላም እየሆነች ከሆነ ከዉጭ እናግዝ የሚል ብዙ ጥያቄ ይቀርብልናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስር ዶር አብይ አሕመድ ፤ በዉጭ ሃገራትን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በተቻለ መጠን የሚልኩትን ገንዘብ በባንክ በኩል እንዲያደርጉም ይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የበጀት ዓመት ሳይሆን የቅድመ ድልድልን በሚመለከት በቀረበላቸዉ ጥያቄ መሰረት ማስረዳታቸዉን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ በዘገባዉ ገልፆልናል።  

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አዜብ ታደሰ

አርያም ተክሌ