1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ10,000 በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተመረቁ

ቅዳሜ፣ የካቲት 27 2013

በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ዮንቨርስቲዎች የተለያዩ ስልጠናዎችን የወሰዱ 10 000 የበጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን ዛሬ የኢትዮጵያ የሰላም ሚኒስቴር አስመርቋል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ባሰሙት ንግግር «የመከላከያ ሰራዊቱ እና የፌደራል ፖሊስ ብዙ ወጣቶች እንዲቀላቀሉት ይፈልጋል።

https://p.dw.com/p/3qIsU
Äthiopien Freiwilliger Jugendabschluss in Addis Abeba
ምስል Y. Gebre/Egziabher/DW

Ber. Volenteer youth graduation Minstry of peace - MP3-Stereo

የ10,000 በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተመረቁ

 በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ዮንቨርስቲዎች የተለያዩ ስልጠናዎችን የወሰዱ 10 000 የበጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን ዛሬ የኢትዮጵያ የሰላም ሚኒስቴር አስመርቋል። ለስልጠናው ከ 100 ሺ በላይ ወጣቶች አመልክተው እንደነበረ የሰላም ሚኒስትሯ ተናግረዋል።  በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ባሰሙት ንግግር «የመከላከያ ሰራዊቱ እና የፌደራል ፖሊስ ብዙ ወጣቶች እንዲቀላቀሉት ይፈልጋል።ይህም ከቅርብ እና ከሩቅ ብዙ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚፈልጉ ኃይሎች ስላሰፈሰፉ ነው ብለዋል። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኘው የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ዮሀንስ ገብረእግዚያብሔር ተመራቂ ወጣቶችም አነጋግሮ ተከታዮን ዘገባ ልኮልናል። 
ዮሀንስ ገብረእግዚያብሔር
ልደት አበበ