ዛሬም የቀጠለው የሲዳማ ምርጫ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 15 2013ማስታወቂያ
በሲዳማ ክልል ትናንት አጋጥሞ በነበረው የድምፅ መስጫ ወረቀት እጥረት ሳይመርጡ የቀሩ ዘጠኝ መቶ ሺህ የሚጠጉ መራጮች ዛሬ ድምጻቸውን ሰጡ። ዛሬ በሁለተኛ ቀን ድምፅ የመስጠቱ ሂደት የተከናወነው የወረቀት እጥረቱ ባጋጠመባቸው 1,998 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ነው። በሌላ በኩል ትናንት ድምፅ የሰጡ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ዛሬ በጣቢያ ደረጃ ይፋ የተደረጉ የቆጠራ ውጤቶችን ሲመለከቱ ውለዋል።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ሸዋዬ ለገሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ