1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አይ ኤም ኤፍ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ28 የዓለም ደሃ ሀገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ አጸደቀ

ማክሰኞ፣ መስከረም 26 2013

ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ28 የዓለም ደሃ ሀገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ አጸደቀ። የገንዘብ ድጋፉ ሀገራቱ ዕዳቸውን እንዲያቃልሉ  እና የኮሮና ወረርሽኝ ያስከተለባቸውን ተጽዕኖ መቋቋም እንዲችሉ ታስቦ መሆኑን ድርጅቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ባለፈው የሚያዝያ ወር ተመሳሳይ የገንዘብ ድጋፍ ለ25ደሃ ሀገራት አድርጎ ነበር።

https://p.dw.com/p/3jUQX
Washington The International Monetary Fund IMF | IWF Hauptquartier
ምስል Reuters/Y. Gripas

ወረርሽኝ ያስከተለባቸውን ተጽዕኖ መቋቋም እንዲችሉ ታስቦ መሆኑን ድርጅቱ  ይፋ አድርጓል። ድርጅቱ ባለፈው የሚያዝያ ወር  ለ25 ሐገራት ተመሳሳይ የገንዘብ ድጋፍ አድርጎ ነበር።ድርጅቱ አሁን ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ሀገራቱ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ለአለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት IMF ለሚከፍሉት ዕዳ ፋታ የሚሰጥ  እና ወረርሽኙን ለመከላከል  የሚያስችል አስቸኳይ የጤና አገልግሎት እንዲያውሉት የሚሰጣቸውን ገንዘብ  ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።  የገንዘብ ድጋፉ ከሚደረግላቸው ውስጥ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሃያ ሁለቱ አፍሪካውያን ሀገራት ናቸው። አፍጋኒስታን ፣ የመን ፣ ሃይቲ ፣የሶሎሞን ደሴቶች እና ታጃኪስታን ድጋፉ ከሚደረግላቸው ሃገራት ውስጥ ናቸው። የዕዳ እፎይታ ጊዜም  ሆነ የገንዘብ ድጋፉን የሚያገኙት ሀገራት በተፈጥሮም ሆነ ሰው ሰራሽ አደጋዎች ውስጥ ያሉ፣ በኮሮና ወረርሽኝ ብርቱ ጉዳት የደረሰባቸው እና ፍጹም ተጋላጭ  ደሃ የሆኑ ሃገራት ናቸው። ማሊ የገንዘብ ድጋፉን ማግኘት የሚገባት ሀገር እንደሆነች የገለጸው ድርጅቱ አሁን ሀገሪቱን በማስተዳደር ላይ ያለው ወታደራዊ መንግስት በአለምአቀፉ ማሕበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት አለማግኘቱ እስኪረጋገጥ ድረስ ድጋፉን የማይለቅ መሆኑን አረጋግጧል።ድርጅቱ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ውስጥ  1.4 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ለሀገራቱ ለመስጠት እንደሚሰራም አስታውቋል።

ታምራት ዲንሳ

ነጋሽ መሐመድ