1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወጣቱ በግብርና የማይሰማራበት ችግር ላይ ውይይት ተካሄደ

ሐሙስ፣ ኅዳር 11 2012

በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሀገራትን ያካተተው ቡድን ሰባት ተብሎ የሚጠራው ስብስብ ተወካዮች ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት ከሚገኙ የተለያዩ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ወጣት አርሶ አደሮች ጋር በአዲስ አበባ ተወያይተዋል። ስብሰባውን በበላይነት ያስተባበረችው የቡድን ሰባት የወቅቱ ሊቀመንበር የሆነችው ፈረንሳይ ነች።

https://p.dw.com/p/3TUbt
Elfenbeinküste Bananenplantage
ምስል Getty Images/AFP/I. Sanogo

ወጣቶች በግብርና የማይሰማሩባቸው ችግሮች ላይ ውይይት ተካሄደ

በአፍሪካ በተለይ በኢትዮጵያ የነገው የግብርና ዘርፍ በወጣቶች የሰው ኃይል ላይ መመስረት እንዳለበት በመታመኑ ቡድን ሰባት ተብሎ የሚጠራው በኢንዱስትሪ የበለጸጉ ሀገራት ስብስብ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶታል። የቡድን ሰባት ተወካዮች ከአፍሪካ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት የተውጣጡ እና አርአያ ይሆናሉ ከተባሉ ወጣቶች ጋር ጉድለቶች ናቸው የሚባሉትን ለይቶ ለማውጣት በአዲስ አበባ ውይይት አካሄደዋል። በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ የዘንድሮው የቡድን ሰባት ሊቀመንበር ፈረንሳይ እንደመሆኗ በአውሮፓ ህብረት የዘርፉ ተጠሪ ኦርያን ባርቴሌሜ ስብሰባው መካሄድ ያስፈለገበትን ምክንያት ለዶይቼ ቬለ አብራርተዋል።   

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

ተስፋለም ወልደየስ 
ማንተጋፍቶት ስለሺ